ኢሚግሬሽን ጥሪን ተቀብለው የሚመጡ እንግዶቹን ለመቀበል ተዘጋጅቻለሁ አለ!

ኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የ “ 1 ሚለየን ወደ አገር ቤት “ ጥሪን ተቀብለው የሚመጡ እንግዶቹን ለመቀበል ተዘጋጅቻለሁ አለ::

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 30 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት እንግዶቹን ለመቀበል የተለያዩ ዝግጅቶችን እያደረገ መሆኑ የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙጂብ ጀማል ገለፁ፡፡

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው እንዲመጡ ጥሪ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው።

በዚሁ መሰረት ትውልደ ኢትዮጵያዊ የታደሰም ሆነ የአገልግሎት ጊዜው ያለፈበት መታወቂያ ያላቸው፥ እንዲሁም በልዩ ሁኔታ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሆኑ ያለ ቪዛ ወደ ኢትዮጵያ መግባት እንደሚችሉ ተገልጿል።

holdbarhet nespresso kapsler
vinglas boda nova
qatar airways handgepäck gewicht
חוק רמקולים תחת כיפת השמיים
כורסא אגורה
nike tech fleece tapered joggers in blue
dámské jarni kotníkové boty tamaris
best apple watch bands for women
dežna obleka za otroke
spodnje hlače moške
fiitgonline.com

ተጓዦች የታደሰም ሆነ ጊዜው ያለፈበትን መታወቂያ አውሮፕላን ማረፊያ በኢሚግሬሽን ካውንተር ላይ ስለሚጠየቁ በእጃቸው ሊይዙ እንደሚገባ ዋና ዳይሬክተሩ መልዕክት አስተላልፈዋል።

የሌላ አገር ፓስፖርት የያዙና የትውልደ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ አገልግሎት ለማግኘት የሚፈልጉ ትውልደ ኢትዮጵያውያን እና በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የፓስፖርት እድሳት አገልግሎት ለማግኘት አስፈላጊ ሰነዶችን በማዘጋጀት http://xn--www-86o.digitalinvea.com/ድረ ገጽ ላይ ማመልከት ይችላሉ ተብሏል።

ከዚህ በፊት የትውልደ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ የሌላቸው ደንበኞች ፥ የቪዛ አገልግሎት ለማግኘት በ www.evisa.gov.et ድረ ገጽ ላይ በማመልከት በሂደቱ ለሚያጋጥማቸው ችግር support@evisa.gov.et በሚል የኢሜል አድራሻ ላይ ጥያቄ ማቅረብ እንደሚችሉም የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት መረጃ ያመላክታል።

ጥሪ በተደረገበት የጊዜ ገደብ ውስጥ ወደ አገር ቤት ለሚገቡ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የመዳረሻ ቪዛ /on arrival visa/ አገልግሎት የሚሰጥ ይሆናል።

የቪዛ ጥያቄ በተቋሙ ህጋዊ ድረ ገጽ www.evisa.gov.et ላይ ብቻ እንደሚሰጥም ዋና ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

አካባቢዎን ይጠብቁ!
ወደ ግንባር ይዝመቱ!
መከላከያን ይደግፉ!

 

Recommended For You

About the Author: admin